በዉይይቱ የኦዲት ሥራዉ ጥራት ባለዉ ሁኔታ ፣ የተሻለ አፈጻጸም እንድኖር፣ የኦዲት ስነ-ምግባር በተላበሰ መልኩ ሥራዎች መሠራት እንዳለባቸዉ፣ ከኦዲት ተደራጊ ተቋማት ጋር ጤናማ የሆነ ሥራንና ሥራን ብቻ መሠረት ያደረገ ግንኝነት መኖር እንዳለበት ክብርት ዋና ኦዲተሯ ገልፀዋል።
በዉይይቱ ላይ የተገኙ ኦዲተሮች በበኩላቸዉ በበጀት ዓመቱ በመ/ቤቱ የተሠጣቸዉ ሥራ በአግባቡ በተሰጣቸዉ ጊዜ በዕቅድ መሠረት እንደሚሰሩ ገልፀዉ ፣ መንግስት በአሁኑ ወቅት ለመንግስት ሰራተኞች የጨመረው ደመወዝ በሥራቸው ላይ መነቃቃትን እንደፈጠረላቸዉ ተናግረዋል። የኦዲት ሥነ -ምግባርን በተላበሰ መልኩ እንደሚሰሩ መግባባት ላይ ተደርሠዋል።
